Monday, July 06, 2009

 

ብርቱካንን ከማሰር አይነት ጎጂ ድርጊት መቼ ነዉ ኢሕአዴግ የሚገደበዉ ? ከድርጅቱ ደጋፊ


ግርማ ካሳ (muziky68@yahoo.com)

ሰኔ 29 ቀን 2001

አባ መላ በሚል ስም የሚታወቁትና አፍቃሪ-ኢሕአዴግ የሲቪሊቲ ፓልቶክ ክፍልን የሚያንቀሳቅሱ የገዢዉ ፓርቲ ደጋፊ (ምናልባትም ባለሥልጣን) አንድ ከፍተኛ የኢሕአዴግ አመራር አባላትን ሲጠይቁ ከተናገሩት የሚከተልዉ ይገኝበታል።

«አንዳንድ ጊዜ ከኢሕአዴግ በኩል፣ በዳያስፖራዉ የኢሕአዴግን ደጋፊዎች ሁሉ ሳይቀሩ፣ criticise የሚያደርጉት popular ያልሆኑ ነገሮችን ትወስዳላቹህ። አላስፈላጊ የሆነ። ለምሳሌ በቅርቡ በብርቱካን ሚደቅሳ ላይ የተወሰደዉ እርምጃ ምንም እንኳን ጥፋት አጥፍታለች ቢባልም ቴክኒካሊ፣ አስፈላጊ ያልሆነ confrontation ነዉ። ብዙ የምንሰራዉ፣ እንደ አገር የምንሰራዉ ብዙ ነገር አለ። በሕግ አንጻር ሁሉን ነገር እንደ ሌጦ መተርጎም የለብንም። ሌሎች moral values የሕዝብ አስተያየት የመሳሰሉ ነገሮችን ግምት ዉስጥ አስገብቶ ማየት ይገባል። የአንድ ጠንካራ መንግስት መለኪያዉ እርሱ ነዉ ብለን እናምናለን። ምን አልባት እነዚህን የመሳሰሉ ነገሮች፣ implication ያላቸዉን ጉዳዮች avoid ለማድረግ ኢሕአዴግ በኩል አንዳንድ ድክመት አለ። በሕዝብ ታዋቂ የሆኑ በጥሩም ሆነ በመጥፎ ተወዳጅነት ያላቸዉ የሙዚቃ ሰዉ ሊሆን ይችላል። ስፖርተኛ ሊሆን ይችላል። ወይም የፖለቲካ ሰዉ። በተለይ የብርቱካን ጉዳይ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ታሪክ ዉስጥ እርስዎም እንደሚያወቁት፣ የሴቶች ታጋዮች ሚና በጣም በጣም ትንሽ ነዉ። በተቃዋሚም እንኳን ብትሆን «በሕጋዊና በሰላማዊ መንገድ እታገላለሁ» ብላ የገባች እስከሆነች ድረስ፣ በአምጽ የሚታገሉትን ተቃዉመን፣ ጠመንጃ ከሻቢያ ጋር አንስተዉ ግለሰቦችን ለመግደል፣ ተቋሞችን ለማፍረስ፣ የሚንቀሳቀሱትንም እያወገዝን፣ በሰላም «አገሬ ዉስጥ ሕግና ሕገ መንግስት አለ። መንግስትን ፊት ለፊት እታገላለሁ» ብሎ የገባዉንም ኃይል እኩል treat ማድረግ የለብንም። በተለይ ሴት በመሆኗ፣ የልጅ እናትም በመሆኗ በኢትዮጵያ ዉስጥ የሴቶችን ሚና ከፍ ለማድረግ ከፍተኛ እምነት አለዉ ብዬ ስለማምን፣ ኢሕአዴግ በእንደዚህ አይነት ሰዎች ላይ የምትወስዱት እርምጃ በምንም መልክ defend ልናደርግ justify ልናደርግ እያቃተን ነዉ። ከእንደዚህ አይነት unpopular ድርጊት መቼ ነዉ ኢሕአዴግ የሚገደበዉ? ይሄን ጉዳይ በቅርቡ ለመፍታት የታሰበ ነገር አለ ወይ ?»


እኝህ ሰዉ፣ የሚደግፉት ፓርቲ ሕግን እንደሌጦ እየተረጎመ አላስፈላጊ ጎጂ ሥራዎችን እየሰራ እንደሆነ ነዉ የሚነግሩን። በተለይም በወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ ላይ የተወሰደዉ እርምጃ እንዳሳዘናቸዉ አበ መላ በድፍረት ገልጸዋል።

በዚች መጣጥፍ ሕግን እንደሌጦ የመተርጉሙ ጉዳይ ላይ አንዳንድ ሃሳቦች ለመስጠት እሞክራለሁ።በቅርቡ አቶ መለስ ዜናዊ ለአገር ዉስጥ ጋዜጦኞች በሰጡት ቃለ መጠይቅ ሰፋ ባለ ሁኔታ በወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ ጉዳይ ላይ ሃተታ አቅርበዋል። ከኢሕአዴግ ደጋፊዎችና ከሌሎች፣ ወ/ት ብርቱካን ሚድቀሳ እንዲፈቱ የሚጥይቁ ብዙ ደብዳቤዎች እንደደረሳቸዉና እርሳቸዉም የወ/ት ብርቱካን መታሰር እንዳሳዘናቸዉ በቃለ መጠይቁ ወቅት ገልጸዋል።

«ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ ይፈቱ» ብለዉ ከሚጠይቁት ደብዳቤዎች መካከል አንዳንዶቹ ሰብአዊነትን ከግምት ዉስጥ በማስገባት፣ ሌሎች ደግሞ «ኢሕአዴግን ይጎዳል፣ የዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታዉን ወደ ኋላ ይጎትታል» በሚል እንደሆነ አቶ መለስ አስረድተዉ፣ የወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ ጉዳይ ግን የሕግ ጉዳይ በመሆኑ ምንም ማድረግ እንዳልተቻለ ነበር የተናገሩት።

ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ ይቅርታ ካገኙ በኋላ ይቅርታ አልጠየኩም እንዳሉ፣ ይቅርታ አልጠየኩም በማለታቸዉ ደግሞ ከዚህ በፊት ይቅርታ ሲሰጣቸዉ አጭበርብረዉ ነበር ማለት እንደሚቻል፣ በማጭበርበር የተገኘ ይቅርታ ደግሞ በሕጉ መሰረት መሰረዝ እንዳለበት ነበር አቶ መለስ የተናገሩት። ይህንን ሲናገሩ ፡

«የይቅርታ ዉሳኔ ለይቅር ተባዩ ከደረሰና ተቀባይነት ካገኘ በኋላ የይቅርታ ዉሳኔ በማጭበርበር ወይም በማታለል የተገኘ መሆኑ ከተረጋገጠ የይቅርታ ዉሳኔዉ ዋጋ አይኖረዉም

የሚለዉን የይቅርታ ሥነ ሥርዓት አዋጅ ቁጥር 395፣ አንቀጽ 16 ፣ንኡስ አንቀጽ 2 አስበዉ እንደሆነ እገምታለሁ።

እዚህ ላይ ነዉ እንግዲህ ሁኔታዎችን ያላገናዘበ፣ የአገርን ጥቅም ከግምት ዉስጥ ያላስገባ፣ በይቅርታ ሥነ ሥርዓት አዋጅ ቁጥር 395 ዉስጥ ያሉትን ሌሎች አንቀጾችን ሁሉ ያልተመለከተ በነጠላዉ፣ አባ መላ እንዳሉት፣ እንደሌጦ የሆነ የሕግ ትርጓሜ ነዉ የምናየዉ።በመጀመሪያ ደረጃ ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ «ይቅርታ አልጠየኩም” አላሉም። ቃሌ በሚለዉ ጽሁፋቸው ለሁለተኛ ጊዜ ከመታሰራቸዉ ከአንድ ቀን በፊት፣ ይቅርታ መጠየቃቸዉን በግልጽ አስቀምጠዋል።

«በሽማግሌዎች የእርቅ ማግባቢያ መንፈስ መሰረት በፖለቲካ የተቀሰቀሰዉን ክስ ፖለቲካዊ እልባት ለመስጠት በማሰብ ለእርቅ ስል ከሌሎች የፓርቲዉ (ቅንጅት) መሪዎች ጋር ተስማምቼ ሰኔ 11 ቀን 1999 ዓ.ም በተጻፈዉ ሰነድ በሽማግሌዎች አማካኝነት ይቅርታ ጠይቄአለሁ። ይህ ብፈልግም ልለዉጠዉ የማልችለዉ ሐቅ ነዉ»


ነበር ያሉት።

በሁለተኛ ደረጃ በወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ ላይ የተወሰደዉ እርምጃ የይቅርታ ሕጉን አላማ ያላንጸባረቀ እርምጃ ተደርጎ የሚወሰድ ነዉ። የይቅርታ ሥነ ሥርዓት አዋጅ ቁጥር 395 አንቀጽ 11 የይቅርታው ዓላማ ምን እንደሆነ በማያሻማና በማያከራክር መልኩ በግልጽ አስቀምጦታል። አንቀጽ 11 እንዲህ ያላል ፡

“የይቅርታ አላማ የሕዝብን ደህንነትና ጥቅም ማስከበር ነዉ” ።

በአንቀጽ 11 መሰረት በወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ ላይ የተወሰደዉ እርምጃ ቢመዘን ምን ያህል የሕዝብን ደህንነትና የአገርን ጥቅም ያስከብራል የሚል ጥያቄን ብናነሳ የኢትዮጵያን ሁኔታ የሚከታተል ማንኛዉም ሰዉ የሚመለሰዉ ነዉ።

ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ በኢትዮጵያ ዉስጥ ያለዉን የአገሪቱን ሕግ በመከተል፣ ሰላማዊ የፖለቲካ እንቅስቃሴ እያደረጉ የነበሩ ሴት ናቸዉ። በሕግ የተመዘገበ የአንድ አብይ የፖለቲካ ፓርቲ፣ አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ሊቀመንበር ናቸዉ። በ1999 ዓ.ም ማለቂያ ወቅት ከቃሊቲ እሥር ቤት ከተፈቱ ጊዜ ጀምሮ ለሁለተኛ ጊዜ እሥር ቤት እስከገበቡበት ጊዜ ድረስ የተከሰሱበት አንዳች ወንጀል የለም። የርሳቸዉ መታሰር በምንም መልኩ የአገርን ደህንነትና ጥቅም ከማስከበር አንጻር የሚያመጣዉ አዋንታዊ ድርሻ የለም።

ይልቅስ የወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ መታሰር ዜጎች በሰላማዊ ትግል ላይ ያላቸዉ ተስፋ እንዲሞነሙን አድርጓል። ብዙዎች ተስፋ ከመቁረጣቸዉ የተነሳ ወደ ጠመንጃ ትግል ፊታቸዉን እያዞሩ ነዉ። በኢትዮጵያዉያን ዘንድ መከፋፈሉና ጥላቻዉ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ ሲሆን ድህነትንና እንደ አልሻባብ ያሉ ሽብርተኞችን በጋራ እንዳንመክት መተማመንና አንድነት ከመካከላችን እየጠፋ ነዉ።

«ሕግ እንደሌጦ መተርጎም ቆሞ፣ ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ በአስቸኳይ ይፈቱ። የፖለቲካ ምህዳሩን ይስፋ» እላለሁኝ። አባ መላ ያሉትን በመጥቀስ ኢሕአዴግ ከጎጂ ድርጊቶች ለራሱ፣ ለሕዝብ፣ ለአገርና ለተተኪዉ ትዉልድ ሲል እንዲቆጠብ እጠይቃለሁ።

በጋራ በፍቅር አገቻችንን አሁን ካለችበት የድህነት አዝቅት፣ የወርደት ካባ እናወጣት።


http://peacewithkinijit.tripod.com/sibhat.wma

Comments:
Please, explain more in detail [url=http://cgi3.ebay.fr/eBayISAPI.dll?ViewUserPage&userid=acheter_levitra_ici_1euro&achat-levitra]acheter levitra en france[/url] It goes beyond all limits.
 
remarquablement, l'information trГЁs amusante acheter cialis generique cialis [url=http://www.ci2s.org/node/1]cialis generique[/url]
je FГ©licite, vous Г©tiez visitГ©s par l'idГ©e brillant simplement http://www.ci2s.org cialis [url=http://www.ci2s.org]cialis[/url]
 
Est d'accord, cette idГ©e excellente faut tout juste Г  propos http://runfr.com/acheter-cialis-et-viagra-sur-le-net-bon-marche-bonuses viagra sur le net acheter cialis
 
Assolutamente d'accordo con lei. In questo nulla in vi e credo che questa sia un'ottima idea. [url=http://lacasadicavour.com/tag/cialis-online/ ]cialis acquistare [/url]Penso che si sbagliano. cialis vendita Questa ГЁ una frase divertente
 
Post a Comment



<< Home

This page is powered by Blogger. Isn't yours?